ኡልትራ አጭር አቆጣጠር
From Wikipedia, the free encyclopedia
ኡልትራ አጭር አቆጣጠር (አብልጦ አጭር አቆጣጠር) ማለት በታሪክ ሊቃውንት ከተገመቱት የጥንት (ከ1000 ዓክልበ. በፊት) ዘመን አቅጣጠሮች መካከል አንዱ ነው።
ከ1000 ዓክልበ. ያሕል በኋላ ለሆነው ታሪክ፣ በተወሰነ አመት ይህ ድርጊት ሆነ ለማለት በጣም አጠያያቂ አይደለም። ከዚያ አስቀድሞ ግን መዝገቦች በካሳውያን ዘመን ጥቂት ስለ ነበሩ፣ ትንሽ 'ጨለማ ዘመን' ተብሏል። በ«ኡልትራ አጭር አቆጣጠር» ዘንድ፣ በ1507 ዓክልበ. የሐቲ (የኬጥያውያን) ንጉስ 1 ሙርሲሊ ባቢሎንን ዘረፈ፤ ከዚያ ካሳውያን ከተማውን ይዘው ስሙን ካራንዱንያሽ አሉት።