ሰኞ፣ ኖቬም 10 2025
Remove ads
Most read


ጥሩነሽ ዲባባ
ጥሩነሽ ዲባባ በመስከረም 21 ቀን 1978 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በአርሲ ክፍለ ሀገር በቼፋ ወረዳ ከኦሮሞ ብሄረሰብ ተወለደች። ጥሩነሽ ለቤተሰብዋ ከአምስቱ 3ኛ ናት። የጥሩነሽ አስተዳደግ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነች። ነገር ግን የጥሩነሽ ቤተሰቦች የረጅም ርቀት አትሌቶች ናቸው። አክስቷ ደራርቱ ቱሉ ሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ እና አንድ ጊዜ ደግሞ የ 10000 ሜትር አሸናፊ እና የብዙ አገር አቋራጭ ውድድር አሸናፊ ነበረች። ሌላ አክስቷም በቀሉ ዲባባ ጥሩ ሯጭ ነበረች ጥሩነሽ ልጅ እያለች በበቆጂ ስትኖር። ሌላዋ እህትዋ እጅጋየሁ ዲባባ ከጥሩነሽ ቀደም ብላ መሮጥ ጀምራ ነበር። ጥሩነሽ ዲባባ የቤተሰብዋን ፈለግ መከተል የጀመረችው እድሜዋ ከፍ ካለ በኋላ ነው። ጥሩነሽ ዲባባ ከ ሯጭ ቤተሰብ ብትፈጠርም ለመሮጥ ግን ምንም ፍላጎት አልነበራትም። ቱሉ በባርሴሎና ኦሎምፒክ በ 10000 ሜትር ባሸነፈች በሰባት አመቱ ጥሩነሽ ወደ አዲስ አበባ በ 2000 ዓ/ም መንገድ ጀመረች። ነገር ግን በቀሉ ዲባባ አባል ከሆነችበት ከእስረኞች ማረሚያ ፖሊስ ቡድን ስፖርት መስሪያ ክበብ ውስጥ አስመዝግባት ልምምድ ቀጠለች። ጥሩነሽ ዲባባ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ምርጥ የረጅም ርቀት ሯጮች አንዷ ለመሆን በቃች። ጥሩነሽ ዲባባ በ 14 አመት እድሜዋ በጣም ወጣት እና ሰውነትዋም ተሰባሪ ይመስል ነበር። ብዙዎችም በሩጫ ምንም ተስፋ እንደሌላት እና ሩጫው የሚጠይቀውን ጠንካራ ሰውነት የላትም ብለው ያምኑ ነበር።
ጥሩነሽ ዲባባ የኢትዮጵያ የረጅም ርቀት ተወዳዳሪ አትሌት ናት። በ 5000ሜትር የአለም ክብረ ወስን ባለቤት ስትሆን በ5000 ሜትር እና በ10000 ሜትር የኦሎምፒክ ውድድር አሸናፊ ናት። ጥሩነሽ አራት የአለም አቀፍ ውድድር እና አምስት የአገር አቋራጭ ውድድር አሸነፊ ናት። በቅጽል ስም “የሕጻን ፊት ያላት ደምሳሽ” በማለት ይጠሩዋታል።
134 views
ሥነ-ፍጥረት
ሰው ከምን ተፈጠረ
ሥነ-ፍጥረት ማለት ልዑል እግዚአብሔር በእውቀቱ ሰማይን፣ ምድርን፣ እንዲሁም በእነርሱ ውስጥ የሚገኙትን ሁሉ ከምንም ወይም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ ብቁ ንቁ የሆኑ ሥነ-ፍጥረት የፈጠረበትን ሁኔታና ሥርዓት የምንማርበት ትምህርት ነው፡፡ ሥነ-ፍጥረት ማለት የፍጥረት መበጀት ማለት ነው፡፡ ይህ የሚታየው ዓለምና በውስጡ ያለው ሁሉ ከዚህ የሚታየው ዓለም ውጭም ያለው የማይታይ ዓለምና በውስጡ ያሉት ረቂቃን ፍጥረታት ሁሉ በእግዚአብሔር ተፈጥረዋል፡፡ /ዘፍ.1፣1 መዝ.101፣25 ኢሳ.66፣1-2 ዕብ.11፣3/ እግዚአብሔር ግዙፉንና ረቂቁን ዓለም የፈጠረው ከምንም ተነስቶ የሚያግናኛቸውና የሚያዋህደው ነገር ሳይኖረው/እምኀበ አልቦ/ ነው፡፡ /መዝ.32፣9 2ኛ መቃ.14፣10 ጥበብ.11፣18 የሐ.ሥራ 17፣24 ዕብ.11፣3 መዝ.148፣5እግዚአብሔር ፍጥረታትን የፈጠረው ሰውንና መላእክትን ስሙን ለመቀደስ ክብሩን ለመውረስ ሲሆን የተቀሩትን ፍጥረታት ግን ለአንክሮ ለተዘክሮ ለምግበ ስጋ ለምግበ ነፍስ ነው። /መዝ.148፣1-3 ራዕ4፣11 የሐ.ሥራ14፣17 ሮሜ.1፣20/
እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሁሉ ፈጥሮ ያከናወነው በስድስት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ /ዘፍ2 እና ዘጸ.20፣9-11/ በእነዚሀ ቀናት የተፈጠሩት ፍጥረታት እያንዳንዳቸው ቢቆጠሩ ፍጡር ተናግሮ አይፈጽመውም ነበር፡፡ ነገር ግን በባሕርያቸው በአኗኗራቸው በ22 ይመደባሉ፡፡ ኩፋሌ 3፣9 የተፈጠሩትም በሦስት መንገድ ነው፡፡ ይኸውም፡-በዝምታ /በአርምሞ/
በመናገር /በነቢብ/
በመስራት /በገቢር/ ናቸው፡፡
106 views


ቅዱስ ያሬድ
የኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ካህንና የዜማና የድርሰት ሊቀ ሊቃውንት
አባታችን ቅዱስ ያሬድ ሚያዝያ ፭ ቀን በ፭፻፭ ዓ.ም በአክሱም ከተማ ተወለደ፡፡ አባቱ አብዩድ ወይም ይስሐቅ ይባላል እናቱ ክሪስቲና ወይም ታውክልያ ትባላለች።
ቅዱስ ያሬድ በተወለደ በ7 ዓመቱ አባቱ ስለሞተ እናቱ የአክሱም ገበዝ ለነበረው ለአጎቱ ለጌዴዎን እንዲያሳድገውና እንዲያስተምረው አደራ ሰጠችው፡፡
101 views


ደራርቱ ቱሉ
የኦሮሞ ብሄረሰብ አባል የሆነችው ደራርቱ ቱሉ በኢትዮጵያ አርሲ ደጋማ አካባቢዎች ከብት በመጠበቅ ነው ያደገችው። እስከ 16 ዓመቷ ድረስ ከወትሮው በተለየ ፈጣ
ደራርቱ ቱሉ በ10ሺ ሜትር የኦሎምፒክየመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ለአፍሪካ ያስገኘች ድንቅዬ ኢትዮጵያዊት ናት።
92 views
Show more



