ሰኞ፣ ኖቬም 10 2025

Remove ads
Most read
Thumbnail
Thumbnail

ጥሩነሽ ዲባባ

ጥሩነሽ ዲባባ በመስከረም 21 ቀን 1978 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በአርሲ ክፍለ ሀገር በቼፋ ወረዳ ከኦሮሞ ብሄረሰብ ተወለደች። ጥሩነሽ ለቤተሰብዋ ከአምስቱ 3ኛ ናት። የጥሩነሽ አስተዳደግ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነች። ነገር ግን የጥሩነሽ ቤተሰቦች የረጅም ርቀት አትሌቶች ናቸው። አክስቷ ደራርቱ ቱሉ ሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ እና አንድ ጊዜ ደግሞ የ 10000 ሜትር አሸናፊ እና የብዙ አገር አቋራጭ ውድድር አሸናፊ ነበረች። ሌላ አክስቷም በቀሉ ዲባባ ጥሩ ሯጭ ነበረች ጥሩነሽ ልጅ እያለች በበቆጂ ስትኖር። ሌላዋ እህትዋ እጅጋየሁ ዲባባ ከጥሩነሽ ቀደም ብላ መሮጥ ጀምራ ነበር። ጥሩነሽ ዲባባ የቤተሰብዋን ፈለግ መከተል የጀመረችው እድሜዋ ከፍ ካለ በኋላ ነው። ጥሩነሽ ዲባባ ከ ሯጭ ቤተሰብ ብትፈጠርም ለመሮጥ ግን ምንም ፍላጎት አልነበራትም። ቱሉ በባርሴሎና ኦሎምፒክ በ 10000 ሜትር ባሸነፈች በሰባት አመቱ ጥሩነሽ ወደ አዲስ አበባ በ 2000 ዓ/ም መንገድ ጀመረች። ነገር ግን በቀሉ ዲባባ አባል ከሆነችበት ከእስረኞች ማረሚያ ፖሊስ ቡድን ስፖርት መስሪያ ክበብ ውስጥ አስመዝግባት ልምምድ ቀጠለች። ጥሩነሽ ዲባባ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ምርጥ የረጅም ርቀት ሯጮች አንዷ ለመሆን በቃች። ጥሩነሽ ዲባባ በ 14 አመት እድሜዋ በጣም ወጣት እና ሰውነትዋም ተሰባሪ ይመስል ነበር። ብዙዎችም በሩጫ ምንም ተስፋ እንደሌላት እና ሩጫው የሚጠይቀውን ጠንካራ ሰውነት የላትም ብለው ያምኑ ነበር። ጥሩነሽ ዲባባ የኢትዮጵያ የረጅም ርቀት ተወዳዳሪ አትሌት ናት። በ 5000ሜትር የአለም ክብረ ወስን ባለቤት ስትሆን በ5000 ሜትር እና በ10000 ሜትር የኦሎምፒክ ውድድር አሸናፊ ናት። ጥሩነሽ አራት የአለም አቀፍ ውድድር እና አምስት የአገር አቋራጭ ውድድር አሸነፊ ናት። በቅጽል ስም “የሕጻን ፊት ያላት ደምሳሽ” በማለት ይጠሩዋታል።
134 views

ኃይሌ ገብረ ሥላሴ

ሀይሌ ገብረ ስላሴ

ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ እ.ኤ.አ ሚያዝያ 18 ቀን 1973 ተወለደ፡፡ ኃይሌ የረጅም ርቀት የአትሌቲክስ ሯጭ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ የተዋጣለት ነጋዴ ባለሀብት ነው፡፡ ኃይሌ ሁለት የኦሎምፒክ ውድድሮች ተሳትፎ በ10,000 ሜትር ሩጫ ሁለት የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያዎችን እና አራት የዓለም አሸናፊዎችን አሸንፏል። ኃይሌ በበርሊን ማራቶን አራት ጊዜ በተከታታይ ያሸነፈ ሲሆን፤ በዱባይ ማራቶንም ሶስት ተከታታይ ድሎችን አስመዝግቧል። በቤት ውስጥም አራት የአለም ዋንጫዎችን አግኝቶ የ2001 የአለም ግማሽ ማራቶን አሸናፊ ሆኗል። ሀይሌ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ከ1,500 ሜትር ርቀት እስከ ማራቶን ድረስ ባሉት ርቀቶች ተወዳድሯል፡፡ በዚህም መሰረት በቤት ውስጥ፣ በጎዳና ላይ እና በአገር አቋራጭ ሩጫዎች ተወዳድሮ አሸንፏል። ከ800 ሜትር እስከ ማራቶን 61 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክብረወሰኖችን በመስበር 27 የአለም ክብረወሰኖችን አስመዝግቧል፡፡ በዚህም ድሉ በታሪክ መዝገብ ላይ ከታላላቅ የረጅም ርቀት ሯጮች አንዱ ነው ተብሎ ተመዝግቧል።
111 views
Thumbnail
Thumbnail

ሥነ-ፍጥረት

ሰው ከምን ተፈጠረ

ሥነ-ፍጥረት ማለት ልዑል እግዚአብሔር በእውቀቱ ሰማይን፣ ምድርን፣ እንዲሁም በእነርሱ ውስጥ የሚገኙትን ሁሉ ከምንም ወይም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ ብቁ ንቁ የሆኑ ሥነ-ፍጥረት የፈጠረበትን ሁኔታና ሥርዓት የምንማርበት ትምህርት ነው፡፡ ሥነ-ፍጥረት ማለት የፍጥረት መበጀት ማለት ነው፡፡ ይህ የሚታየው ዓለምና በውስጡ ያለው ሁሉ ከዚህ የሚታየው ዓለም ውጭም ያለው የማይታይ ዓለምና በውስጡ ያሉት ረቂቃን ፍጥረታት ሁሉ በእግዚአብሔር ተፈጥረዋል፡፡ /ዘፍ.1፣1 መዝ.101፣25 ኢሳ.66፣1-2 ዕብ.11፣3/ እግዚአብሔር ግዙፉንና ረቂቁን ዓለም የፈጠረው ከምንም ተነስቶ የሚያግናኛቸውና የሚያዋህደው ነገር ሳይኖረው/እምኀበ አልቦ/ ነው፡፡ /መዝ.32፣9 2ኛ መቃ.14፣10 ጥበብ.11፣18 የሐ.ሥራ 17፣24 ዕብ.11፣3 መዝ.148፣5እግዚአብሔር ፍጥረታትን የፈጠረው ሰውንና መላእክትን ስሙን ለመቀደስ ክብሩን ለመውረስ ሲሆን የተቀሩትን ፍጥረታት ግን ለአንክሮ ለተዘክሮ ለምግበ ስጋ ለምግበ ነፍስ ነው። /መዝ.148፣1-3 ራዕ4፣11 የሐ.ሥራ14፣17 ሮሜ.1፣20/ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሁሉ ፈጥሮ ያከናወነው በስድስት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ /ዘፍ2 እና ዘጸ.20፣9-11/ በእነዚሀ ቀናት የተፈጠሩት ፍጥረታት እያንዳንዳቸው ቢቆጠሩ ፍጡር ተናግሮ አይፈጽመውም ነበር፡፡ ነገር ግን በባሕርያቸው በአኗኗራቸው በ22 ይመደባሉ፡፡ ኩፋሌ 3፣9 የተፈጠሩትም በሦስት መንገድ ነው፡፡ ይኸውም፡-በዝምታ /በአርምሞ/ በመናገር /በነቢብ/ በመስራት /በገቢር/ ናቸው፡፡
106 views
Show more