ልድያ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ልድያ (አሦርኛ፦ ሉዱ፤ ዕብራይስጥ፦ לוד /ሉድ/፣ ግሪክ፦ Λυδία /ሉዲያ/) በምዕራብ ትንሹ እስያ የተገኘ ታሪካዊ አውራጃና መንግሥት ነበር።
በታወቀበት ዘመን ዋና ከተማው ሰርዴስ ሆነ። በአንድ ወቅት የትንሹ እስያ ምዕራብ ክፍል በሙሉ የሉድያ ግዛት ነበረ። በኋለ ዘመን ደግሞ ልድያ የሮማ መንግሥት ጠቅላይ ግዛት ነበረ። መሐለቅ መጀመርያ የተፈጠረው በልድያ ክ.በ. 660 አመት ያሕል እንደ ነበረ ይታመናል።