ታምራት ሞላ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ታምራት ሞላ ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ዘፋኝ ሲሆን ብዙ ዘመናዊና ባህላዊ የሙዚቃ ስራወችን በማቅረብ ይታወቃል። በ፳፻ ዓ.ም የካንሰር በሽታ የተገኘበት ድምጻዊ ታምራት በህክምና ከህመሙ ሙሉ በሙሉ እንደ ተሻለው አሳውቆ የነበረ ቢሆንም ህመሙ እንደገና አገርሽቶበት በተወለደ በ፮፱ አመቱ በየካቲት ፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። የቀብር ሥነ ሥርዓቱም በዕለቱ በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተሰቦቹ ፣ ወዳጅ ዘመዶቹ ፣ የሙያ አጋሮቹ እና አድናቂዎቹ በተገኙበት ተፈጸሟል [1]።