ፑንት
From Wikipedia, the free encyclopedia
ፑንት (ፕወነት)[1] ከጥንታዊ ግብጽ ጋራ ንግድ ያካሄድ የነበረ ሀገር ነበር። ግብጻዊ ተጓዦችና መርከበኞች ከዚያ ወርቅ፣ ሙጫ፣ ቆጲ፣ የዝሆን ጥርስ፣ ባርያዎችና አውሬዎች ያመጡ ነበር። ፑንት ደግሞ አንዳንዴ «ታ ነጨር» (ሀገረ አምላክ) ይባላል።[2]
ፑንት በቀይ ባሕር ዳርቻ ወይም በአፍሪቃ ወገን[3] ወይም በአረቢያ ወገን[4]ወይም ምናልባት በሁለቱም እንደ ተገኘ ይታሰባል።
በአንዳንድ ዘመናዊ መምህሮች ዘንድ ፑንት ከፉጥ (የካም ልጅ) ጋር መታወቂያ ሊኖረው ይችላል።[5]በተለመደው ልማድ ግን ይህ ፉጥ በቀይ ባሕር አካባቢ ሳይሆን በሊብያ ነበር የሠፈረው።