ሌፍኮዚያ

From Wikipedia, the free encyclopedia

ሌፍኮዚያ
Remove ads

ሌፍኮዚያ (Λευκωσία, Lefkoşa) የቆጵሮስ ዋና ከተማ ነው።

Thumb
የነጻነት አደባባይ

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 197,600 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 35°09′ ሰሜን ኬክሮስ እና 33°21′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ሌፍኮዚያ በጥንት ሌድራ የተባለ ከተማ-አገር ነበር። የሌድራ ንጉስ ኦናሳጎራስ ለአሦር ንጉስ አስራዶን በ680 ክ.በ. ቀረጥ እንደ ገበሩ ይመዘገባል። 300 ክ.በ. ገዳማ በግብጽ ንጉሥ 1 ፕቶሎማዮስ ልጅ በሌኮስ አዲስ ተሰርቶ ስሙ ደግሞ ሌፍኮጤያ ሆነ። በግሪክና ሮማውያን ዘመኖች ትልቅ መንደር አልነበረም። በ340 ዓ.ም. መጀመርያ ኤጲስ ቆፖሱን ትሪፊሊዮስን ባገኘው ጊዜ ስሙ ሌድሪ ወይም ሌፍኩሲያ ተባለ።

Thumb
ሌፍኮዚያ በቆጵሮስ ውስጥ

በወደቦቹ ላይ አደጋ በአረቦች ስለ ተጣለ ሰዎችም ወደ ሌፍኮዚያ ስለ ሸሹ ከተማው በትልቅነት አደገና በ10ኛ ክፍለ ዘመን ገዳማ የደሴቱ ዋና ከተማ ሆነ። በ1184 ዓ.ም. ፈረንጆች (የመስቀል ጦርነት ሠራዊት) ያዙትና ስሙን ኒኮሲያ አሉት። ስለዚህ እስከ ዛሬ ድረስ በምዕራባውያን አገራት ቦታው 'ኒኮሲያ' ይባላል።

Remove ads
Loading related searches...

Wikiwand - on

Seamless Wikipedia browsing. On steroids.

Remove ads