ኃይሌ ገብረ ሥላሴ
ሀይሌ ገብረ ስላሴ From Wikipedia, the free encyclopedia
Remove ads
ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ እ.ኤ.አ ሚያዝያ 18 ቀን 1973 (1965 ዓ.ም) ተወለደ፡፡ ኃይሌ የረጅም ርቀት የአትሌቲክስ ሯጭ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ የተዋጣለት ነጋዴ ባለሀብት ነው፡፡ ኃይሌ ሁለት የኦሎምፒክ ውድድሮች ተሳትፎ በ10,000 ሜትር ሩጫ ሁለት የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያዎችን እና አራት የዓለም አሸናፊዎችን አሸንፏል። ኃይሌ በበርሊን ማራቶን አራት ጊዜ በተከታታይ ያሸነፈ ሲሆን፤ በዱባይ ማራቶንም ሶስት ተከታታይ ድሎችን አስመዝግቧል። በቤት ውስጥም አራት የአለም ዋንጫዎችን አግኝቶ የ2001 የአለም ግማሽ ማራቶን አሸናፊ ሆኗል። ሀይሌ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ከ1,500 ሜትር ርቀት እስከ ማራቶን ድረስ ባሉት ርቀቶች ተወዳድሯል፡፡ በዚህም መሰረት በቤት ውስጥ፣ በጎዳና ላይ እና በአገር አቋራጭ ሩጫዎች ተወዳድሮ አሸንፏል። ከ800 ሜትር እስከ ማራቶን 61 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ክብረወሰኖችን በመስበር 27 የአለም ክብረወሰኖችን አስመዝግቧል፡፡ በዚህም ድሉ በታሪክ መዝገብ ላይ ከታላላቅ የረጅም ርቀት ሯጮች አንዱ ነው ተብሎ ተመዝግቧል።
ኃይሌ በ2008 ዓ.ም በበርሊን በተደረገው የማራቶን ውድድር በ2:03:59 ሰዓት በመግባት የራሱን ክብረ ወሰን በ27 ሰኮንዶች በማሻሻል ጭምር አሸንፏል፡፡ ይህ ክብረ ወሰን ለሦስት ዓመታት ያህል ሳይሻሻል ቆይቷል። ኃይሌ እ.ኤ.አ. ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ በ10,000 ሜትር በአዋቂዎች የዕድሜ ምድብ የዓለም ክብረ ወሰንን እስካሁን እንደያዘ ነው፡፡
በሜዳ እና በጎዳና ሩጫ ውድድር ባደረጋቸው የተለያዩ አስገራሚ ድሎች ምክንያት ብዙዎች “የረጅም ርቀት ሩጫ ንጉሥ” ብለው ይጠሩታል። ኃይሌ እ.ኤ.አ. በ2011 ዓ.ም በኒው አፍሪካን ከ100 ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪ አፍሪካውያን መካከል አንዱ ሆኖ ተጠቅሷል።
እ.ኤ.አ. በ2020 (2012 ዓ.ም) ታዋቂው የኦሮሞ ዘፋኝ ሃጫሉ ሁንዴሳ በሞተበት ወቅት በተፈጠረው ግርግር ወቅት የኦሮሞ ተወላጆች ቁጣቸውን የገለጡት ኦሮሞ ባልሆኑ ዜጎች የንግድ ድርጅቶች እና ንብረቶች ላይ ነበር። በዚህም ግርግር የኃይሌ ሆቴሎች እና ሪዞርቶች ተቃጥለዋል፡፡ 400 ሰራተኞችም ስራ አጥተዋል።
Remove ads
Wikiwand - on
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Remove ads