From Wikipedia, the free encyclopedia
ሙሉቀን መለስ (፲፱፻፬፭ ዓ.ም. ተወለደ[1]) የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወርቃማ ዘመን ዘፋኖች መሃል አንዱ ነው። 1960 ና 1970ዎቹ በርካታ ዘመናዊ ዘፋኞች የታዩበት ወቅት ነበር። ሙሉቀን መለስን ለየት የሚያደርው ቢኖር ባሀላዊውን ከዘመናዊው በማዋሃድ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ለማሳደግ ያደረገው ጥረት ነው።
የዚህ መጣጥፍ የማያደላ ዝንባሌ ያለው ሁናቴ መኖሩ አጠያያቂ ጉዳይ ነው። (መግለጫውን በውይይት ገጽ ላይ ይፈልጉ።) |
ሙሉቀን መለስ ባሁኑ ጊዜ በአሜሪካን አገር በዋሽንግተን ዲሲ ሙሉ ጊዜ የፕሮቴስታንት ሃይማኖት አገልጋይ ሲሆን ያለውን ድንቅ ችሎታ ላመነበትና ለሚያምንበት ሃይማኖት አውሎ አሁንም እጹብ ድንቅ ድምጽ ካላቸው የመንፈሳዊ ዘማሪዎችም አንዱ ነው።
ሙሉቀን መለሰ በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ገና የ፲፫ ዓመት ልጅ እያለ ድምጻዊነት ሙያውን በፈጣን ኦርኬስትራ በመጀመር በ፲፱፻፷ ዓ.ም. ወደ ፖሊስ ኦርኬስትራ ክፍል ገብቶ ዝነኛነቱን አሳውቋል። ሙሉቀን በሙዚቃ ዓለም በነበረበት ጊዜ በርካታ ዜማዎች የተጫወተ ሲሆን ዜማዎቹም በሸክላ ተቀርጸው ወጥተዋል።[1]
«እናቴ ስትወልደኝ መች አማከረችኝ፤ የፊት ጉዴን ትታ እደግ ማሞ አለችኝ» የተባለችው ዜማ የመወደድዋን ያህል ድምጻዊው ሙሉቀን መለሰም ተደናቂ ሆኗል። ሙሉቀን መለሰ እንደዚሁም፦ «ወንበር ተደግፎ ክብ ጠረጴዛ የሰነፎች በትር ትችት በጣም በዛ» እያለ የሚጫወታት ዘፈንም ሙሉቀንን ታዋቂና ዘፈኖቹንም ተወዳጅ አድርጎታል።[1]
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Every time you click a link to Wikipedia, Wiktionary or Wikiquote in your browser's search results, it will show the modern Wikiwand interface.
Wikiwand extension is a five stars, simple, with minimum permission required to keep your browsing private, safe and transparent.