ሳውል በብሉይ የወጣለት ዕብራዊ ስሙ ሲሆን ፣ ጳውሎስ በሐዲስ የወጣለት ነው ትርጉሙም ብርሃን ማለት ነው ። በተርሴስ (ዛሬ በቱርክ ውስጥ) ከሚቀመጥ ከአንድ ሸማኔ ተወልዶ ካደገ በኋላ በኢየሩሳሌም ኦሪትን ከገማልኤል ተማረ። ስለኦሪትና ስለሙሴ ከፍ ያለ ቅናት፤ በዘመኑ ስለተፈጠረው የክርስትና ሃይማኖት የበዛ ጥላቻ ነበረው። ስለዚህ ክርስቲያኖችን ማባረር፤ ማሰር፤ ማጉላላት ሥራዬ ብሎ ይዞት ነበር።

Quick Facts ቅዱስ ጳውሎስ መልክተኛው, የክርስቶስ ምርጥ ዕቃ ...
ቅዱስ ጳውሎስ
መልክተኛው
Thumb
የክርስቶስ ምርጥ ዕቃ
ስም መጀመሪያ ሳውል በኋላ ጳውሎስ
የተወለደው ቦታ ተርሴስ በሮሜ መንግሥት
የተወለደበት ዘመን በ፩ኛው ክፍለዘመን ፭ኛው ዓመት
የሚታወቀው በመልክቱ፣ ከይሁድነት ወደ ክርስቲያንነት በመቀየሩ ፣ በሰማዕትነቱ
ያረፈበት ፩ኛው ክፍለ ዘመን ፷፬፣፷፭፣ ፷፯ ዓ.ም. በሰይፍ ተሰይፎ
ሥራው ድንኳን ሰራተኛ፣ ለአህዛብ የክርስቶስን ወንጌል ሰባኪ፣ መልክት ጸሐፊ
የሚከበረው በመላው የክርስትና ሃይማኖት እምነት ተከታይ
ንግሥ ሐምሌ ፭
Close

ለዚሁ ጉዳይ ወደ ደማስቆ ሲሄድ እከተማይቱ ሊደርስ ሲል የሚያንፀባርቅ ብርሃን መታውና ወደቀ።

Thumb
ጳውሎስ በደማስቆ መንገድ

በመሬት ላይ እንደተኛ በሰማይ ካለው ከኢየሱስ ጋራ፤ አሳብ ለአሳብ እንደዚህ ሲል ተለዋወጠ።

ኢየሱስ፦ ሳውል ሳውል ለምን ታሳድደኛለህ ? ሳውል፦ አንተ ማነህ አቤቱ ? ኢየሱስ፦ እኔ ኢየሱስ ነኝ አንተ የምታሳድደኝ ። በተሳለ ብረት ላይ ብትረግጥ ላንተ ይብስብሃል ። ሳውል፦ ምን እንዳደርግ፤ ትፈቅዳለህ ? ኢየሱስ፦ ወደ ደማስቆ ከተማ ግባ፤ ልታደርገው የሚገባህን ሐናንያ ይነግርሃል ።

የሐዋ፡ሥራ፡ም፡ ፱ ፣ ቁ፡ ፬-፮

በዚህ ዓይነት ጳውሎስ ክርስትናን የተቀበለው ከክርስቶስ ነው ማለት ይቻላል። ዝርዝር ነገር ከሐናንያ ማጥናቱ እርግጥ ነው። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ፍጹም ክርስቲያን፤ ትጉህ ሐዋርያ ሆነ። ያለ ዕረፍት የግሪኮችና የሮማውያን አማልክት እነዘውስ እነአርጤሚስ የአሶራውያንና የሲዶናውያን አማልክት እነአስታርት እነበዓል የገነኑባቸውን ከተሞች ያለዕረፍት እየዞረ የነዚያን ከንቱነት፤ የክርስቶስን አዳኝነት በቃልም፤ በጽሕፈትም መሰከረ። ለአባቶቹ ለዕብራውያንም በብሉይ ሐዲስ መተካቱን ለመንገር አልፈራም። ስለክርስቶስና ስለወንጌል በኢየሩሳሌም ተገረፈ፤ በቂሣርያ ታሠረ፤ በሮማ በሰይፍ አንገቱን ተቆርጦ ሞተ።

ነገር ግን በደረሰባቸው ከተሞች ሁሉ ክርስቶስን ሳያሳምን ቤተ ክርስቲያን ሳይመሠርት አያልፍም ነበር። ፲፬ መልዕክቶችንሲጽፍ፤ ከኢየሩሳሌም ግሪክ፤ ከግሪክ ሮማ፤ እየተመላለሰ የሐዋርያነት ሥራውን ሲያከናውን ራሱ ድንኳን እየሰፋ የራሱን መሮሪያ ራሱ ይችል ነበር እንጂ ከሰው ድካም የመነጨ ወይንና ምግብ በርሱ፤ ጉሮሮ አላለፉም ማለት ነው። ደንበኛ ሐዋርያነቱን ከሚያስረዱት ከብዙ ሥራዎቹ ውስጥ አንደኛው ይህ ነው።

:

Wikiwand in your browser!

Seamless Wikipedia browsing. On steroids.

Every time you click a link to Wikipedia, Wiktionary or Wikiquote in your browser's search results, it will show the modern Wikiwand interface.

Wikiwand extension is a five stars, simple, with minimum permission required to keep your browsing private, safe and transparent.