አሪያኒስም
From Wikipedia, the free encyclopedia
አሪያኒስም ወይም የአሪያን ቤተ ክርስቲያን በአንድ ክርስቲያን ቄስ አሪዩስ (250-328 ዓም) ትምህርቶች የተመሠረተ በሥላሴ የማያምን ሀረ ጤቃዊ የተባለ እምነትና እንቅስቃሴ ነበር።
አሪዩስ እንዳስተማረ ኢየሱስ ክርስቶስ ወይም ወልድ ከእግዚአብሔር አብ በታች የተለየና የተፈጠረ አምላክ እንደ ነበር አለ፣ እንጂ ሥላሴን አላስተማረም። እግዚአብሔር ከዓለም በፊት ኢየሱስን ቢፈጥርም፣ ኢየሱስ ግን ያልኖረበት ጊዜ ነበር፤ ከአብ በታች የተለየ ንዑስ አምላክ ነው ብሎ ያስተምር ነበር።
አሪዩስ ካረፈ በኋላ አሪያኒስም ለጊዜው በምሥራቁ የሮሜ መንግሥት እየተደገፈ እምነቱ ወደ አንዳንድ ጀርመናዊ ብሔር ተስፋፍቶ ነበር፤ ለጥቂት ዘመናት እስከ 663 ዓም ድረስ ቆየ። የ«አሪያኖች» ስም ከመሥራቹ አሪዩስ የተሰየመ ሲሆን፣ አሁን አንዳንድ ያልተማሩ ሰዎች «አርያኖች» ከሚለው ሕንዳዊ-ኢራናዊ ስያሜ ጋራ ተስተዋቸዋል፤ በውኑ ግን «አሪያኖች» ከ«አርያኖች» ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም።