From Wikipedia, the free encyclopedia
አዲስ ዘመን በደቡብ ጎንደር የሚገኝ ከተማ ሲሆን ከባሕር ዳር ወደ ጎንደር ከተማ በሚጓዘው መንገድ መካከል ይገኛል። በድሮ ስሙ ደብረ አብርሃም ሲባል፣ በአሁኑ ጊዜ የከምከም ወረዳ አስተዳደር ማዕከል በመሆን ያገለግላል።
አዲስ ዘመን | |
አዲስ ዘመን ከተማ | |
ከፍታ | 1975 ሜትር |
የሕዝብ ብዛት | |
• አጠቃላይ | 24,849 |
ከአዲስ ዘመን ከተማ አጠገብ ከሚገኙ ታዋቂ ቦታዎች የደብረ ገላውዲዎስ ገዳም፣ የዋሻ እንድሪያስ፣ ዋሻ ተክለሃይማኖት አብያተ ክርስቲያናት እና አስባ ተራራዎች ይገኛሉ። ታሪካዊው ጉዛራም እንዲሁ በቅርብ ይገኛል። ደብረ ገላውዲዎስ በዓፄ ገላውዲዎስ ዘመን በነበረ ቅዱስ ሰው የተመሰረተ ሲሆን በቆዩ የግድግዳ ምስሎቹና ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በሚመነጩ የወይራ ዛፎቹ ይታወቃል። በኋላ በ1572ዓ.ም. አንድ የኦሮሞ ነገድ በንጉሱ በዓፄ ሱሰንዮስ ላይ ዘመቻ ሲከፍት የዓፄ ሠርፀ ድንግል እናት ወደዚህ ቦት ደብረ አብርሃም መጥታ እንደተጠለለች ታሪክ ይዘግባል[1]።
አዲስ ዘመን፣ ከ1956-1972 ዓ.ም የሊቦ አውራጃ ማዕከል በመሆንም አገልግሏል። በ1958 በተደረገ የህዝብ ቆጠራ አዲስ ዘመን ውስጥ 4400 ሰዎች የነበሩ ሲሆን፣ ከደብረ ማርቆስ የሚመጣው የስልክ አገልግሎት እዚህ ከተማ ደርሶ ነበር። በአጠቃላይ 3 ቢሮዎች እና 2 ግለሰቦች የስልክ አገልግሎት ተጠቃሚ ነበሩ።
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Every time you click a link to Wikipedia, Wiktionary or Wikiquote in your browser's search results, it will show the modern Wikiwand interface.
Wikiwand extension is a five stars, simple, with minimum permission required to keep your browsing private, safe and transparent.