ሞሪሸስ
From Wikipedia, the free encyclopedia
Remove ads
ሞሪሸስ በሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ በማዳጋስካር አጠገብ የተገኘው ደሴት አገር ነው። ከ፩ ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉበት። በ1960 ዓም ነፃነት ከዩናይትድ ኪንግደም አገኘ።
እስከ 1673 ዓም ድረስ ሕልውና የነበረው የታላቅ ወፍ ዝርያ ዶዶ በሞሪሸስ ብቻ ይገኝ ነበር፤ በዚያውም ወቅት መጨረሻው የዶዶ ወፍ አለቀ። የሰው ልጆች ግን እስከ 1500 ዓም ያህል ድረስ አልኖሩበትም። ከዚያ የኔዘርላንድና የፈረንሳይ ሰዎች ይሠፈሩበት ነበር።
ሸንኮራ ኣገዳ የሞሪሸስ ዋነኛ ምርት ነው፤ ከዚህም አረቄ ይሠራል። ኗሪዎቹ አሁን በብዛት ከሕንድ ስለ ሆኑ፣ ከግማሽ በላይ የሂንዱ ሃይማኖት ተከታዮች ናቸው። የተወደዱት እስፖርቶች እግር ኳስና ራግቢ ናቸው።
| ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
Remove ads
Wikiwand - on
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Remove ads

