ይግባ ጽዮን
የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከ1285 እስከ 1294 From Wikipedia, the free encyclopedia
Remove ads
ዓፄ ይግባ ጽዮን በዘውድ ስማቸው ቀዳማዊ ሰለሞን ከ1285 - 1294 (እ.ኤ.አ) ሲነግሱ ከአባታቸው ይኩኖ አምላክ ጋር ከንግስናቸው በፊት አገሪቱን አብረው አስተዳድረዋል።
==
==
የዘመኑ ተጓዥ ማርኮ ፖሎ እንደጻፈ
በዚህ ንጉስ ዘመን የነበረው ታዋቂው የአውሮጳ ተጓዥ ማርኮ ፖሎ ስለአጠቃላይ የኢትዮጵያ ግዛትና በተለይ ንጉሱ በአዳል ላይ ያደረገውን ውጊያ በ1290 ባሳተመው መጽሃፉ ላይ ጠቅሷል[1]፡
እንደሰማሁት፣ በ1288 የሃበሻው ንጉስ ወደ እየሩሳሌም በመሄድ የኢየሱስ ክርስቶስን መቃብር ለመሳለም ፈልጎ የሱ መኮንኖች ይህ የሚያስከትለውን ችግር በተለይ የእስልምና ተከታይ መንግስታት በአካባቢ መብዛትን ግምት ውስጥ በማስገባት በሱ ምትክ በሃይማኖተኛነቱ ይደነቅ የነበረ ጳጳስ እንዲሄድ አድርጎ ይህ ጳጳስ እየሩሳሌም በመሄድ ስለት አስገብቷል። ጳጳሱ ሲመለስ ግን አዳል ውስጥ ተማርኮ የአዳሉ መሪ ጳጳሱ እስልምና እንዲቀበል ቢመክረው እምቢ በማለቱ ጳጳሱ እንዲገረዝ [እንዲሰለብ?] አደረገ። ከዚያም ጳጳሱ ወደ አገሩ ከተመለሰ በኋላ የተደረገበትን ግፍ ለንጉሱ ነገረው። ንጉሱም ወዲያው ፈረሱን አስጭኖ ከሰራዊቱ ጋር አዳልን ለማጥፋት ዘመተ። የአዳሉም ልዑል የአቢሲኒያ ጦር እንደዘመተበት በሰማ ጊዜ ሁለት ባለ ብዙ ሰራዊት እስልምና ተከታይ ንጉሶች ከእንዲረዱት ጥሪ አደረገ። ነገር ግን የሃበሻው ንጉስ ስላሸነፋቸው የኤደንን [አዳል?] ዋና ከተማ [ዘይላ?] በመቆጣጠር ከተማይቱን በዘበዘ። ይህም ለጳጳሱ የተደረገበትን ጉዳት ለመበቀል ነበር።
Remove ads
የእስልምና መስፋፋት
በዚህ ድል ምክንያት ሰላም በመገኘቱ የእስልምና ተከታይ የሆኑ ነጋዴወች ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያውን ውስጠኛውን ክፍል ዘልቀው ለመግባትና ለመነገድ ክፍተት አገኙ፣ በብዛትም በአገሪቷ ለመሰራጨት ቻሉ። [2] ይህ በዚ እንዳለ እስልምና በሃድያ፣ ሶማሊያ፣ ሐረር፣ይፋት እና ዳህላክ ደሴቶች ከዚህ ንጉስ ዘመን በፊት ስር የሰደደ ቢሆንም፣ በአፋር ፣ አርሲና ሲዳሞ መሰበክና መስፋፋት የጀመረው በዚህ ዘመን ነበር። አርጎባም በእስልምና ስር የወደቀው በዚህ ዘመን ነው። የወላስማ ሥርወ መንግሥት በይፋት የተነሳው በ1285 በዚህ ጊዜ ነው፤ ቀስ ብሎም አዳዲሶቹን ክፍለ ሃገሮች፦ ፈተገርን፣ ዳዋሮን እና ባሌን በተጽዕኖው ስር ለማስገባት ቻለ።[3] በትግራይ] ውስጥ የእስልምና ተከታዮች መሰባሰቢያ የሆነው ነጋሽ እየጎለመሰ ሄደ።
Remove ads
የመንግስት ሽግግር
በጥንቱ የኢትዮጵያ ነገስታት የነበረው ቋሚ ችግር፣ ስልጣንን የማወርስ ችግር ነበር። ይግባ ጺዮን 5 ወንድ ልጆች ነበሯቸው ግን ከ5ቱ የትኛው እንዲነግስ መወሰን ስላልቻሉ እያንዳንዱ ልጅ ለአንድ አመት እንዲነግስ እንዳረጉ ታሪክ ጻህፍት ይዘግባሉ [4]
ማጣቀሻወች
Wikiwand - on
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Remove ads