ስሜን ቆጵሮስ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ስሜን ቆጵሮስ (በይፋ፦ «የቱርክ ስሜን ቆጵሮስ ሪፐብሊክ»፤ ቱርክኛ፦ Kuzey Kıbrıs /ኩዘይ ክብርስ/) በቆጵሮስ ደሴት ላይ የምትገኝ አገር ናት።
በሐምሌ 8 ቀን 1966 ዓም የቆጵሮስ ግሪኮች ወገን የቆጵሮስ መንፈቅለ መንግሥት ስላካሄዱ፣ ስለዚህ በ13 ሐምሌ የቱርክ ሥራዊት በስሜን ወረረ፣ ጦርነቱም ከጨረሰ በኋላ የቱርኮች ወገን አስተዳደር በስሜኑ፣ የግሪኮችም በደቡቡ ቀርተው ነበር። በ1967 ዓም ስሜኑ «የቱርክ ቆጵሮስ ፌዴራላዊ ግዛት» ሆነ፣ በ1976 ዓም «የቱርክ ስሜን ቆጵሮስ ሪፐብሊክ» ሆነ።
ሆኖም ከቱርክ አገር በስተቀር፣ ከአንዳችም ሌላ አገር ምንም ዲፕሎማቲክ ተቀባይነት የለውም። በተረፈ ሌሎቹ አገራት በይፋ በደቡብ የሚገኘውን የቆጵሮስ ሪፐብሊክን ይግባኝ ይቀበላሉ።
ምጣኔ ሀብቱ በተለይ በቱሪስም ይመሰረታል፤ ቱሪስቶቹ ወይም በአየር ከቱርክ አገር፣ ወይም በመርከብ ይገባሉ። በግል ጀልባ (ያሕት) የሚገቡም አሉ። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ምርቶች የወተት ውጤቶች፣ ሎሚ፣ አረቄ፣ ዶሮ፣ ድንች ናቸው። ሕዝቡ ቱርክኛ ይናገራልና የእስልምና ተከታዮች ናቸው። ዋንኛው እስፖርት እግር ኳስ ነው። ባሕላቸው በጭፈራና በሙዚቃ፣ በሥነ ጥበብ፣ በአበሳሰል ወዘተ. እንደ ቱርክ አገር ባሕል ይመስላል።
Wikiwand in your browser!
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Every time you click a link to Wikipedia, Wiktionary or Wikiquote in your browser's search results, it will show the modern Wikiwand interface.
Wikiwand extension is a five stars, simple, with minimum permission required to keep your browsing private, safe and transparent.