አፍሮ እስያዊ ቋንቋዎች
From Wikipedia, the free encyclopedia
አፍሮ እስያዊ ቋንቋዎች በሰሜን አፍሪቃና በደቡብ ምዕራብ እስያ የሚነገሩ ቋንቋዎች ቤተሰብ ሲሆን 6 ንዑሳውያን ቤተሰቦች አሉት።[1] እነዚህም ጥንታዊ ግብጽኛ፣ በርበርኛ፣ ቻዳዊ፣ ኩሻዊ (ሐማዊ)፣ ኦሞአዊና ሴማዊ ቋንቋዎች ናቸው።[1] ከእነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ውስጥ 3ቱ ማለትም ኩሻዊ (ሐማዊ)፣ ኦሞአዊና ሴማዊ ቋንቋዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ይነገራሉ።[1] በዕድሜ ረገድ ግዕዝና ግብጽኛ ጥንታዊ ቋንቋዎች ሲሆኑ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ኩሻዊና ኦሞአዊ መጀመርያ የገቡት፣ ሴማዊ ቋንቋዎች ከእነሱ ቀጥለው ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ናቸው።[1]
የአፍሮሲያቲክ ቋንቋዎች ከሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ተበታተኑ፣ ነገር ግን የመጨረሻው መነሻቸው ከ15,000 ዓመታት በፊት ከምዕራብ እስያ ወደ አፍሪካ በመጣው የፓሊዮሊቲክ የፍልሰት ማዕበል ውስጥ ሲሆን ሁለቱንም “የምእራብ ዩራሺያን የዘር ግንድ” እና ፕሮቶ-አፍሮሲያቲክን አስተዋውቋል።[2][3][4][5]