ደብረ ፀሐይ ቍስቋም ከጎንደር ከተማ በስተ ስሜን ምዕራብ ወጣ ብሎ በሚገኘው ደብረ ፀሐይ የተባለ ተራራ ላይ የተሰራ የቤተክርስቲያንና ቤተመንግስት ግቢ ነው። ደብረ ፀሓይ ቁስቋም በእቴጌ ምንትዋብ፣ ከ1725 ዓ.ም. እስከ በ1738 ዓ.ም. ተገንብቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ዙሪያው በግምብ የታጠረና በ8 እንቁላል ግንቦች የተከበበ ነው[1]። ግቢውን ሰንጥቆ የሚያልፍ ግምብ ደብሩን ለሁለት ሲከፍል አንዱ ጎን ቁስቋም ማርያም የተባለውን ቤተክርስቲያን ሲይዝ ሌላው ጎን ደግሞ የብርሃን ሞገሴን (ምንትዋብን) ቤተመንግስት፣ ስዕል ቤት የተባለውን የምትጸልይበትን ክብ ጸሎት ቤት፣ እንግዶች መጋበዣ ዕልፍኝ፣ ሰፊ የሰራተኞች ግምብ፣ የጄምስ ብሩስቤተመጻሕፍት ተብሎ የሚታወቀው ግምብና ለልዩ ልዩ ግልጋሎት የተመደቡ እንቁላል ግንቦችን ይይዛል። ደብረ ፀሐይ በተመሰረተበት ዘመን የራሱ ጉልት የነበረው ሲሆን ይኼውም በእብናት፣ በለሳ እና አርማጭሆ ተሰባጥሮ ይገኝ ነበር፤ ስለሆነም 260 ቀሳውስትን በስሩ ያስተዳድር ነበር[2]፡፡
| ||||
---|---|---|---|---|
ደብረ ፀሐይ ቁስቋም | ||||
ቁስቋም እልፍኝ - 1876 ዓ.ም. | ||||
አገር | ኢትዮጵያ | |||
ዓይነት | ባሕላዊ | |||
መመዘኛ | c(ii)(iii) | |||
የውጭ ማጣቀሻ | 19 | |||
አካባቢ** | አፍሪካ | |||
የቅርስነት ታሪክ | ||||
ቅርስ የሆነበት ጊዜ | 1971 (3ኛ ጉባኤ) | |||
* በዩ.ኔ.ስ.ኮ ስሙ እንደሰፈረ። ** የዩ.ኔ.ስ.ኮ. ክልል ክፍፍል |
ግቢው ሦስት ጊዜ ጉዳት ደርሶበታል። በመጀመሪያ በ1858፣ ዓፄ ቴዎድሮስ መቅደላ ሊያሰሩት ላሰቡት ቤተ ክርስቲያን ከቤተክርስቲያኑ የተለያዩ ንዋያትን መውሰዳቸው ነበር። ሁለተኛው ጉዳት የደረሰው በ1870ወች፣ የሱዳን ደርቡሾች ግቢውን በእሳት በማጋየት ያደረሱት ዋናው ጉዳት ነበር። በዚህ ቃጠሎ ቁስቋም ማርያም እንዳለ ሊቃጠል ችሏል። በ1932ዓ.ም. የእንግሊዝ ጦር በአውሮፕላን ቦምብ ስለጣለበት፣ እንዲሁ ተጨማሪ አደጋ ደረሰበት። ስለሆነም በአሁኑ ወቅት ብዙ ጉዳት ሳይደርስበት ከሞላ ጎደል ተርፎ የሚገኘው አጥሩና እልፍኙ ነው[3]።
1.ደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያም 2.የቤተክርስቲያን አለቃ መኖሪያ 3.ቁስቋም ዕቃ ቤት 4.ዋናው በር 5.ቤተ ላሕም 6.ስዕል ቤት 7.የምንትዋብ መኖሪያ 8.የምንትዋብ እልፍኝ 9.እልፍኝ በር 11.የቁስቋም ሰገነቶች |
ማጣቀሻ
Wikiwand in your browser!
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Every time you click a link to Wikipedia, Wiktionary or Wikiquote in your browser's search results, it will show the modern Wikiwand interface.
Wikiwand extension is a five stars, simple, with minimum permission required to keep your browsing private, safe and transparent.