ዐይን (ፊደል)
From Wikipedia, the free encyclopedia
ዐ ዑ ዒ ዓ ዔ ዕ ዖ
ዐይን በጥንታዊ አቡጊዳ ተራ 16ኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓን በአራማያ በዕብራይስጥ በሶርያም ፊደሎች 16ኛው ፊደል «ዐይን» ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል «ዐይን» ተብሎ በ«አብጃድ» ተራ 16ኛ ነው።
በመጀመርያው (ግዕዝ) ቅርጽ (አ) በልሳነ ግዕዝ እንደ ሌሎቹ ፊደላት የ«ኸ» አናባቢ ድምጽ ሆነው ነበር፤ በአማርኛ ግን ድምጹ እንደ አራተኛው (ራብዕ) ቅርጽ (ዓ) አንድላይ ነው። በአማርኛ አጻጻፍ ብዙ ጊዜ ከአልፍ (አ) ጋራ ሊለዋውጥ ይችላል። ቀድሞ ግን ድምጾቻቸው የተለያዩ ነበሩ።