ገምል
From Wikipedia, the free encyclopedia
ገ ጉ ጊ ጋ ጌ ግ ጎ ጓ ጐ ጒ
ገምል በአቡጊዳ ተራ ሦስተኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓን በአራማያና በዕብራይስጥ ፊደሎች ሦስተኛው ፊደል «ግመል» በሶርያም ፊደል «ገመል» ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል «ጂም» ተብሎ በ«አብጃድ» ተራ 3ኛ ነው። (በዘመናዊ ተራ ግን 5ኛው ነው።) በግሪክም 3ኛው ፊደል «ጋማ» ይባላል። በነዚህ ቋንቋዎች አጠራሩ «ግ» ሲሆን በዓረብኛ ግን «ጅ» ሆኗል።
የ«ግ» ድምጽ በቋንቋ ጥናት «ነዛሪ የትናጋ ፈንጂ» ይባላል።[1]