From Wikipedia, the free encyclopedia
ኅዳር ፲፱ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፸፱ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፪፻፹፯ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፹፮ ቀናት ይቀራሉ።
፲፭፻፲፫ ዓ.ም. በፈርዲናንድ ማጄላን መሪነት የተቀናጁ ሦሥት የፖርቱጋል መርከቦች በደቡብ አሜሪካ ደቡባዊ ጫፍ የባሕር መስመር አልፈው ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ወደ ሰላማዊ ውቅያኖስ በመሸጋገር የመጀመሪያዎቹ አውሮፓውያን ሆኑ።
፲፰፻፴፮ ዓ.ም. በሐዋይ ደሴቶች የነጻነት ዕለት ነው። የብሪታንያ እና የፈረንሳይ መንግሥታት የሐዋይን ደሴቶች ንጉዛት (ንጉሣዊ + ግዛት)ሉዐላዊነት አወቁ፣ አከበሩ።
፲፱፻፭ ዓ.ም. አልባኒያ ከኦቶማን ግዛትነት ነጻነቷን አወጀች።
፲፱፻፴፮ ዓ.ም. የአሜሪካው ፕሬዚደንት ፍራንክሊን ሩዝቬልት፣ የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስቴር ዊንስተን ቸርቺል እና የሶቪዬት ሕብረት መሪ ጆሴፍ ስታሊን ኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ላይ ተገናኝተው ከናዚ ጀርመን ጋር ለሚያካሂዱት ጦርነት የሕብረት ስልት አውጥተው፣ ተስማምተው ተለያዩ።
፲፱፻፶፩ ዓ.ም. ቅኝ ግዛቶች የነበሩት ቻድ፣ የኮንጎ ሪፑብሊክ እና ጋቦን በፈረንሳይ ቤተሰብ ስር እራሳቸውን ማስተዳደር ጀመሩ።
፲፱፻፶፫ ዓ.ም. ሞሪታንያ ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛትነት ነጻነቷን ተቀዳጀች።
፲፱፻፷፰ ዓ.ም. የፖርቱጋል ቅኝ ግዛት የነበረችው ምሥራቅ ጢሞር፣ ገዥዋ ስትተዋት የራሷን ነጻነት አወጀች። ከዘጠኝ ቀናት በኋላ ግን በኢንዶኔዚያ ሠራዊቶች ተወራ የኢንዶኔዚያ ሃያ ሰባተኛ አውራጃ ሆነች።
፲፱፻፹፫ ዓ.ም. በብሪታንያ “ኮንሰርቫቲቭ” የቀኝ ፖለቲካዊ ቡድን መሪ የነበረችው ማርጋሬት ታቸር ከመሪነቷ ካስወገዷት በኋላ የጠቅላይ ሚኒስቴርነቱን ስልጣን ለአገሪቷ ንግሥት ዳግማዊት ኤልሳቤጥ አስረከበች። ከአሥራ አምሥት ደቂቃ በኋላ ንግሥቲቱ አዲሱን የ”ኮንሰርቫቲቭ” ቡድን መሪ ጆን ሜጀርን አቅርባ፣ አዲስ አስተዳደር በጠቅላይ ሚኒስቴርነት እንዲመራ ሾመችው።
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Every time you click a link to Wikipedia, Wiktionary or Wikiquote in your browser's search results, it will show the modern Wikiwand interface.
Wikiwand extension is a five stars, simple, with minimum permission required to keep your browsing private, safe and transparent.