ሰናኽተንሬ አሕሞስ
From Wikipedia, the free encyclopedia
Remove ads
ሰናኽተንሬ አሕሞስ በላይኛ ግብጽ በ2ኛው ጨለማ ዘመን (17ኛው ሥርወ መንግሥት) ለአጭር ወራት ምናልባት 1567 ዓክልበ. አካባቢ በሂክሶስ ዘመን የገዛ ፈርዖን እንደ ነበረ ይታመናል።
==
==
እስከ 2004 ዓም ድረስ ስሙ «ሰናኽተንሬ» ብቻ ከካርናክ ፈርዖን ዝርዝርና በአንዳንድ መቃብር ተጽፎ ይታወቅ ነበር። በ2004 ዓም ተጨማሪ ቅርሶች ተገኝተው ሌላው ስሙ አሕሞስ (ያሕመስ)፣ የሔሩ ስምም መሪመዓት እንደ ሆነ ታወቀ። የተከታዩ የሰቀነንሬ ታዖ አባት፣ የካሞስና የ1 አሕሞስ አያት እንዲሁም የተቲሸሪ ባለቤት እንደ ሆነ ይገመታል፣ ይህ ግን እርግጥ አይደለም።
ቀዳሚው 7 አንጠፍ |
የግብፅ (ጤቤስ) ፈርዖን 1567 ዓክልበ. ግድም |
ተከታይ ሰቀነንሬ ታዖ |
Remove ads
Wikiwand - on
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Remove ads