መጋቢት ፳፬

From Wikipedia, the free encyclopedia

Remove ads

መጋቢት ፳፬፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፬ኛው ዕለት ሲሆን፤ የበጋ ወቅት ፹፱ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፷፪ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፷፩ ቀናት ይቀራሉ።

ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች

  • ፳፻፲ ዓ.ም. - ዶ/ር ዓቢይ ኣሕመድ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ።
  • ፲፮፻፸፪ ዓ/ም - ድፍን የፀሐይ ጋረዶ በኢትዮጵያ ላይ አለፈ፣ ፀሐይ ጨለመች።
  • ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽና ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴ፣ ንጉሥ ተፈሪ መኮንን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተብለው በንጉሠ ነገሥት ዙፋን ተቀመጡ፡፡

ልደት

ዕለተ ሞት

  • ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ በነገሡ በአሥራ ሦሥት ዓመት ተኩል በ፶፬ ዓመት ዕድሜያቸው ዐረፉ። የሞታቸው ዜና እንደተሰማም በከተማው የሐዘን ጥላ አጠላበት። አባታቸው ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ በተቀበሩበት በታዕካ ነገሥት በዓታ ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ።
  • ፲፱፻፺፯ ዓ/ም - የካቶሊኩ ሊቀ ጳጳስ ዳግማዊ አቡነ ዮሐንስ-ጳውሎስ በ፹፬ ዓመት ዕድሜያቸው አለፉ።

ዋቢ ምንጮች


More information የኢትዮጵያ ወራት ...
Loading related searches...

Wikiwand - on

Seamless Wikipedia browsing. On steroids.

Remove ads