ግንቦት
From Wikipedia, the free encyclopedia
Remove ads
ግንቦት የወር ስም ሆኖ በሚያዝያ ወር እና በሰኔ ወር መኻል የሚገኝ ከአስራ ሦስቱ ኢትዮጵያ የወራት አቆጣጠር ውስጥ ዘጠነኛው የወር ስም ነው።
የግንቦት ቀናት | ||||||
1 | 2 | 3 | 4 | 5 | 6 | 7 |
8 | 9 | 10 | 11 | 12 | 13 | 14 |
15 | 16 | 17 | 18 | 19 | 20 | 21 |
22 | 23 | 24 | 25 | 26 | 27 | 28 |
29 | 30 |
«ግንቦት» ከግዕዙ «ግንባት» ከሚለው ቃል የተባዛ ነው።[1] የግንቦት ወር የክረምት ጎረቤት ቢሆንም ሙቀታማ፣ ደረቃማ እና ዝንብ የሚበዛበት ወር ነው። በዚህም ጸባዩ ብዙ ምሳሌያዊ አነጋገሮችን አፍርቷል።
አባቶች "በግንቦት አንድ ዋንጫ ወተት" ይላሉ። ”ኅብረ ብዕር” በተባለው መጽሐፋቸው፣ አቶ ካሕሣይ ገብረ እግዚአብሔር፣ ብሂሉ ሰውነታችን ኃይለኛውን የግንቦት ሙቀት መቋቋም ይችል ዘንድ አንጀት የሚያርስ፣ ቆዳን የሚያለሰልስ፣ የጠፋ አቅምን የሚመልስ ወተት ማግኘት አለበት ለማለት ነው። ይላሉ
ሌላም ብሂል አለ። "በነሐሴ ባቄላ፣ በግንቦት አተላ" የሚለውም ሰው ብቻ ሳይሆን ከብቶችም በደረቃማው ገጽታ ምክንያት በግንቦት ወር ምን ያህል እንደሚጐዱ ያሳያል። በመሆኑም በወሩ አተላ እንደሚወደድ አመልካች ነው።
ግንቦት ጎልታ የምትታወቀው በተለይ ዓመት ካመት ከልደታ ጋር ነው። ልዩ ክብር አላት፤ ድግስም አላት። ከንፍሮ እስከ ቂጣ ብሎም እስከ እርድ ድረስ ይፈጸምባታል።
በኦሮሞ ሕዝብ ባህላዊ ሥርዐት ደግሞ "ቦረንተቻ" የሚከበርበት ወር ነው። ጐጆ የወጣ ሁሉ ከሠላሳ ቀናት በአንዱ (ራሱ በመረጠው) ድግስ መደገስ አለበት፤ በድግሱ መቅረብ ያለባቸው የድግስ ዓይነቶችም ቂጣ፣ ቆሎ፣ ጉሽ ጠላና በግ ናቸው፤ ለድግሱ የሚታረደው በግ፣ ሙሉ ጥቁር ሆኖ ግንባሩ ላይ ነጭ ምልክት ያለበት መሆንም ይኖርበታል። የድግሱ ሥነ ሥርዓት የሚከናወነው ከመሸ በኋላ ማለትም ከብት በረት ከገባ በኋላ ሲሆን፣ ለዝግጅቱ ተብሎ የሚታረደው የበግ ሥጋ መበላት ያለበት ተጠብሶ ነው። ከዚህ ውጭ ሥጋው በወጥ መልክ ተሠርቶ ወይም በጥሬው መብላት አይፈቀድም።
Remove ads
Wikiwand - on
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Remove ads