መጋቢት ፰

From Wikipedia, the free encyclopedia

Remove ads

መጋቢት ፰፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፹፰ ኛው ዕለት ሲሆን፤ የበጋ ወቅት ፸፫ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፸፰ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፸፯ ቀናት ይቀራሉ።

ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች

  • ፲፰፻፺፪ ዓ/ም - በሩሲያው ንጉሥ ዛር እስክንድር ሣልሳዊ አዲስ አበባ ላይ የተገነባው እና በሩሲያ የቀይ መስቀል ማኅበር ስም የተሠየመው የከተማዋ የመጀመሪያው ሆስፒታል (በኋላ ዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል) ተመርቆ ተከፈተ።
  • ፲፰፻፺፪ ዓ/ም - ዳግማዊ ምኒልክ በአገሪቱ እየጨመረ የመጣውን ሰካራምነት ለመከላከል በሚል ዓላማ ከውጭ የሚገቡትን መጠጦች የሚያግድ አዋጅ አወጁ።
  • ፲፱፻፹ ዓ/ም - የኤርትራ ነጻነት ግንባር ሠራዊት በአፋበት ግንባር በተሰማራው የ’ናደው እዝ’ ጦር ላይ ከጎንና ከኋላም አስርጎ ሲያጠቃ በኮሎኔል ጌታነህ ኃይሌ የሚመራው የናደው እዝ በከፍተኛ ሽብር ሊሸነፍ ቻለ።
Remove ads

ልደት


ዕለተ ሞት

  • ፳፻፬ ዓ/ም - በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ፓትርያርክ ሆነው ከ፲፱፻፷፬ ዓ/ም ጀምሮ ለ፵ ዓመታት የእስክንድርያ (ኮፕት) ቤተ ክርስቲያንን የመሩት መንፈሳዊ አባት አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ በዛሬው ዕለት በተወለዱ በ፹፰ ዓመታቸው አረፉ።

ዋቢ ምንጮች


More information የኢትዮጵያ ወራት ...
Loading related searches...

Wikiwand - on

Seamless Wikipedia browsing. On steroids.

Remove ads