ሰኔ ፳፩፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፺፩ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ/(በልግ)ወቅት ፹፮ተኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፸፭ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፸፬ ቀናት ይቀራሉ።
ታሪካዊ ማስታወሻዎች
- ፲፱፻፮ ዓ/ም - የ አውስትሪያ እና ሁንጋሪያው ዘውድ አልጋወራሽ፣ አውስትሪያዊው አርች ዱክ ፍራንዝ ፈርዲናንድ በዩጎዝላቪያዊ ነፍሰ ገዳይ እጅ ሰኔ ፲፱ ቀን ፲፱፻፮ ዓ/ም መገደል ነው።የአውስትሪያው ልዑል ‘ፍራንዝ ፈርዲናንድ’ እና ባለቤታቸው የሳራዬቮን ከተማ በመጎብኘት ላይ ሳሉ በነፍሰ ገዳይ እጅ ሕይወታቸውን አጡ። ይኼ ድርጊት የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት መንስዔ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል።
- ፲፱፻፲፩ ዓ/ም - የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ተቀናቃኞች፤ በአንድ በኩል አለማኝያ እና በሌላው ወገን የቃል ኪዳን አገራት የጦርነቱን ፍጻሜ ስምምነት የቨርሳይ ውል በዚህ ዕለት ተፈራረሙ።
- ፲፱፻፶፩ ዓ/ም - የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ባስልዮስ ካይሮ ላይ በተካሄደ ሥርዓተ-ሢመት በቅብጡ ፓትርያርክ አቡነ ቄርሎስ ፮ኛ ተቅብተው የፓትርያርክነቱን ዘውድ ደፉ።
- (እንግሊዝኛ) FCO 371/1829 - ANNUAL REVIEW FOR ETHIOPIA FOR 1974
- መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፤ - የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያው ፓትረያርክ (፲፱፻፶፩ ዓ/ም)
Wikiwand in your browser!
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Every time you click a link to Wikipedia, Wiktionary or Wikiquote in your browser's search results, it will show the modern Wikiwand interface.
Wikiwand extension is a five stars, simple, with minimum permission required to keep your browsing private, safe and transparent.