ነሐስ (ፊደል)
From Wikipedia, the free encyclopedia
Remove ads
ነ ኑ ኒ ና ኔ ን ኖ ኗ
ነሐስ በጥንታዊ አቡጊዳ ተራ 14ኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓን በአራማያ በዕብራይስጥ በሶርያም ፊደሎች 14ኛው ፊደል «ኑን» ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል «ኑን» ተብሎ በ«አብጃድ» ተራ 14ኛ ነው።
ታሪክ
የነሐስ መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ የእባብ ስዕል መስለ። ለዚህም ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ ነበር። አጠራሩ ግን «ጀ» ነበር። በግብፅ የሠሩት ሴማውያን ግን በቋንቋቸው «ነሐስ» ስላሉት፣ ይህ ስዕል «ነ» ሆኖ እንዲሰማ መጣ።
የከነዓን «ኑን» እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ የአረብኛም «ኑን» ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት «ኑ» (Ν ν) አባት ሆነ። እሱም የላቲን አልፋቤት (N n) እና የቂርሎስ አልፋቤት (Н н) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ«ነሐስ» ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል። በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥር ፶ (ሐምሳ) ከግሪኩ ν በመወሰዱ እሱም የ«ነ» ዘመድ ነው።
Remove ads
Wikiwand - on
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Remove ads