ዐይን (ፊደል)

From Wikipedia, the free encyclopedia

Remove ads

ዐ ዑ ዒ ዓ ዔ ዕ ዖ



More information የአቡጊዳ ታሪክ ...

ዐይን በጥንታዊ አቡጊዳ ተራ 16ኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥሶርያም ፊደሎች 16ኛው ፊደል «ዐይን» ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል «ዐይን» ተብሎ በ«አብጃድ» ተራ 16ኛ ነው።

በመጀመርያው (ግዕዝ) ቅርጽ (አ) በልሳነ ግዕዝ እንደ ሌሎቹ ፊደላት የ«ኸ» አናባቢ ድምጽ ሆነው ነበር፤ በአማርኛ ግን ድምጹ እንደ አራተኛው (ራብዕ) ቅርጽ (ዓ) አንድላይ ነው። በአማርኛ አጻጻፍ ብዙ ጊዜ ከአልፍ (አ) ጋራ ሊለዋውጥ ይችላል። ቀድሞ ግን ድምጾቻቸው የተለያዩ ነበሩ።

Remove ads

ታሪክ

More information ተመሳሳይ ግብፃዊ ስዕል, ቅድመ-ሴማዊ ...


የዐይን መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ የዐይን ስዕል መስለ። ለዚህም ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ ነበር። አጠራሩ ግን «ኢር» ነበር። በግብፅ የሠሩት ሴማውያን ግን በቋንቋቸው «ዐይን» ስላሉት፣ ይህ ስዕል «ዐ» ሆኖ እንዲሰማ መጣ።

More information ከነዓን, አራማያ ...


ከነዓን «ዐይን» እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ የአረብኛም «ዐይን» ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት «ኦሚክሮን» (ትንሹ ኦ ማለት፣ Ο, ο) አባት ሆነ። እሱም የላቲን አልፋቤት (O o) እና የቂርሎስ አልፋቤት (О о) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ«ዐይን» ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል። በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥር (ሳባ) ከግሪኩ ο በመወሰዱ እሱም የ«ዐ» ዘመድ ነው።

Remove ads
Loading related searches...

Wikiwand - on

Seamless Wikipedia browsing. On steroids.

Remove ads