ድንት
From Wikipedia, the free encyclopedia
Remove ads
ደ ዱ ዲ ዳ ዴ ድ ዶ ዷ
ድንት (ወይም ድልት) በአቡጊዳ ተራ አራተኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓን በአራማያና በዕብራይስጥ በሶርያም ፊደሎች አራተኛው ፊደል «ዳሌት» ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል «ዳል» ተብሎ በ«አብጃድ» ተራ 4ኛ ነው። (በዘመናዊ ተራ ግን 8ኛው ነው።) በግሪክም 4ኛው ፊደል «ዴልታ» ይባላል። በነዚህ ቋንቋዎች ሁሉ አጠራሩ «ድ» ነው።
በአማርኛ ደግሞ «ጀ ጁ ጂ ጃ ጄ ጅ ጆ» ከ«ደ...» ትንሽ ተቀይሯል።
ታሪክ
የድንት መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ ወይም የደጅ ወይም የዓሣ ስዕል መስለ። ለደጅ ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ «ዐእ» ነበር።
የከነዓን «ዳሌት» እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ «ዳሌት» የአረብኛም «ዳል» ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት «ደልታ» (Δ δ) አባት ሆነ፤ እሱም የላቲን አልፋቤት (D d) እና የቂርሎስ አልፋቤት (Д, д) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ«ድንት» ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል። በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥር ፬ (አራት) ከግሪኩ Δ በመወሰዱ እሱም የ«ደ» ዘመድ ነው።
Remove ads
Wikiwand - on
Seamless Wikipedia browsing. On steroids.
Remove ads