አልፍ

አማርኛ From Wikipedia, the free encyclopedia

Remove ads

አ ኡ ኢ ኣ ኤ እ ኦ ኧ



More information የአቡጊዳ ታሪክ ...

አልፍ (ወይም አሌፍ) በአቡጊዳ ተራ መጀመርያው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥና በሶርያ ፊደሎች መጀመርያው ፊደል አሌፍ ይባላል። በዓረብኛ ፊደል ደግሞ መጀመርያው ፊደል አሊፍ ሲሆን በግሪክአልፋ ይባላል።

በመጀመርያ በግዕዝ የዚህ ምልክት ምክንያት ተፈናጣሪ ተናባቢ ድምጽ ለማመልከት ነበር። ይህ ድምጽ ፍች «ነዛሪ የጉሮሮ እግድ» ይባላል።[1] በዛሬው አማርኛ ግን ምንም ተናባቢ ሳይኖር አናባቢ ብቻ ሊያመለከት ይችላል። (በዘመናዊ ዕብራይስጥም «አሌፍ» እንዲህ ይጠቅማል።) በዚህ ጥቅም በአማርኛ አጻጻፍ ብዙ ጊዜ ከዐይን (ዐ) ጋራ ሊለዋውጥ ይችላል።

በአረብኛ ደግሞ «አሊፍ» ከጥንት ተፈናጣሪ ተናባቢ ድምጽ ነበር። በኋላ ግን 'አ' የሚለውን አናባቢ ብቻ ሊያመልከት መጣ። ስለዚህ ነዛሪ የጉሮሮ እግድ ለመጻፍ ሌላ አዲስ ፊደል «ኅምዛ» ተፈጠረ።

በመጀመርያው (ግዕዝ) ቅርጽ (አ) በልሳነ ግዕዝ እንደ ሌሎቹ ፊደላት የ«ኸ» አናባቢ ድምጽ ሆነው ነበር፤ በአማርኛ ግን ድምጹ እንደ አራተኛው (ራብዕ) ቅርጽ (ኣ) አንድላይ ነው። ቢሆንም አንዳንዴ በባዕድ ቃላት ይህ አናባቢ በቃል መጀመርያ ሲጋጠም «ኧ» የሚለው ልዩ ፊደል አለ።

Remove ads

ታሪክ

Loading related searches...

Wikiwand - on

Seamless Wikipedia browsing. On steroids.

Remove ads