ሐምሌ ፪

From Wikipedia, the free encyclopedia

Remove ads

ሐምሌ ፪ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፪ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፷፬ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፷፫ ቀናት ይቀራሉ።

አቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች

፲፭፻፴፫ ዓ/ም - ኢትዮጵያን የወረረውን ግራኝ መሐመድን ለመከላከል የዘመተውን የ|ብርቱጋል ሠራዊት የመራው ኤስቴቫዎ ዳጋማ ወንድሙን ክሪስቶቫዎ ዳጋማ ን ከአራት መቶ ወታደሮችና መቶ ሃምሳ ባሪያዎች ጋር ትቶ ከምጽዋ ወደብ ወደአገሩ ተጓዘ።

፲፱፻፴፱ ዓ/ም - የእንግሊዝ ልዕልት፣ (አሁን ዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ) እና የሌፍተናንት (አሁን የኤዲንበራ መስፍን ልዑል) ፊሊፕ የጋብቻ እጭት ይፋ ተደረገ።

፲፱፻፹፫ ዓ/ም - የደቡብ አፍሪቃ ሪፑብሊክ ለሠላሳ ዓመታት ከተገለለችበት የኦሊምፒክ ማሕበር ተመልሳ አባል ሆነች።

፲፱፻፺፬ ዓ/ም - የቀድሞውን የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የተካው የአፍሪቃ ኅብረት አዲስ አበባ ላይ ተመሠረተ። የደቡብ አፍሪቃው ፕሬዚደንት ጻቦ እምቤኪ የኅብረቱ የመጀመሪያው ሊቀ መንበር ሆነው ተመረጡ።

Remove ads

ልደት

፲፱፻፯ ዓ.ም - ስመ ጥሩው ኢትዮጵያዊ አርበኛ እና የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ሊቀ መንበር የነበሩት ክቡር ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን ቡልጋ፣ ልዩ ስሙ ቡሄ ዓምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ።

፲፱፻፰ ዓ/ም - ከ፲፱፻፷፫ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፷፯ ዓ/ም የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ሰር ኤድዋርድ ሂዝ

፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የቀድሞው የሞሮኮ ንጉሥዳግማዊ ሀሳን(አረብኛ: الحسن الثاني‎)። ንጉሡ የዛሬው የንጉሥ ሞሀመድ ራብእ (አረብኛ: محمد السادس‎) አባት ናቸው።

፲፱፻፴፬ ዓ/ም - ሪቻርድ ራውንድትሪ (Richard Roundtree). ሪቻርድ በዋና ተዋናይነት <<ጆን ሻፍት>> (John Shaft) ሆኖ <<ሻፍት ኢን አፍሪካ>> (Shaft in Africa) በተባለው ፊልም ላይ ከዘነበች ታደሰ (ሸርሙጣ ሆና) እና ደበበ እሸቱ (ዋሳ Wassa) ጋር ሠርቷል፡

Remove ads

ዕለተ ሞት


ዋቢ ምንጮች



More information የኢትዮጵያ ወራት ...
Loading related searches...

Wikiwand - on

Seamless Wikipedia browsing. On steroids.

Remove ads