መስከረም ፳፩

From Wikipedia, the free encyclopedia

Remove ads

መስከረም ፳፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፳፩ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ቀን በኋላ እስከ ዓመቱ ፍጻሜ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፫፻፵፭ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፫፻፵፬ ዕለታት ይቀራሉ።

በዚህ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ማርያምን በዓል በማሰብ ትዘክረዋለች።


ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች

  • ፲፱፻፶፬ ዓ.ም - የምስራቅ እና የምዕራብ ካሜሩን ክፍሎች ተዋህደው፣ የካሜሩን ፌዴራላዊ ሪፑብሊክን መሠረቱ።
  • ፲፱፻፶፬ ዓ.ም - በአሜሪካ የጥቁሮች ሰብዓዊ መብት ትግል ጄምስ መሬዲዝ የተባለውን ጥቁር ተማሪ ወደ ሚሲሲፒ ዩኒቨርሲቲ መግባት በተከሰተው ግጭት ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ሰባ አምሥት ሰዎች ደግሞ የአካል ጉዳት ደረሰባቸው።
  • ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - ለሟቹ የግብጽፕሬዚደንት ጋማል አብደል ናስር የቀብር ስርዓት የወጡ ወደ አምሥት ሚሊዮን የሚገመቱ አዘነተኞች በተነሳ ግርግር እና ግፊያ ብዙ ሰዎች ተጨፍልቀው ሞቱ።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በፊሊፒንስ ከተማ ማኒላ ላይ በተካሄደው የቡጢ ውድድር ሞሐመድ አሊ ባላጋራውን ጆ ፍሬዘርን ከአሥራ አራት ዙር ግብግብ በኋላ በነጥብ ብልጫ አሸነፈ።


Remove ads

ልደት

ዕለተ ሞት


ዋቢ ምንጮች


More information የኢትዮጵያ ወራት ...
Loading related searches...

Wikiwand - on

Seamless Wikipedia browsing. On steroids.

Remove ads